am_tw/bible/other/detestable.md

1.7 KiB

የተጠላ፣ መጥላት

“የተጠላ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው የማይወደድና የተናቀ ነገር ነው። አንድን ነገር “መጥላት” ያንን ነገር አጥብቆ አለመውደድ ማለት ነው።

  • መጽሐፍ ቅዱስ ክፉን ስለ መጥላት ደጋግሞ ይናገራል። ይህም ክፉን አለመውደድና ክፉን መጽሐፍ ማለት ነው።
  • ሐሰተኛ አማልክትን የሚያመልኩ ሰዎች የሚያደርጉትን ክፉ ሥራ አስመልክቶ ሲናገር እግዚአብሔር፣ “የተጠላ” በሚለው ቃል ተጠቅሟል።
  • ጎረቤቶቻቸው የነበሩ አገሮች ያደርጉ የነበረውን ኃጢአትና ርኵሰት እንዲጠሉ እግዚአብሔር እስራኤላውያንን አዝዞአል።
  • ቅጥ ያጣ የግብረ ሥጋ ግንኙነትን እግዚአብሔር፣ “የተጠላ” ብሎታል።
  • ጥንቆላ፣ መተትና ሕፃናትን መሥዋዕት ማድረግ ሁሉ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠሉ ናቸው።
  • “መጥላት” የሚለውን ቃል፣ “አለመውደድ” ወይም፣ “መጸየፍ” ወይም፣ “መናቅ” ብሎ መተርጎም ይቻላል።
  • እርሱ ራሱ፣ “ርኵስ” ያላቸውንና ለምግብነት መዋል እንደሌለባቸው የተናገረላቸው አንዳንድ እንስሳት፣ እንዲጠሉ እግዚአብሔር ለእስራኤላውያን ተናግሮአል። ይህ፣ “በጣም መጸለይ” ወይም፣ “ማስወገድ” ወይም፣ “ተቀባይነት እንደሌለው ነገር መቁጠር” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።