am_tw/bible/other/desolate.md

1.8 KiB

ባድማ፣ ወና ማድረግ

“ባድማ” ወይም “ወና ማድረግ” መኖሪያ የነበረውን ከእንግዲህ መኖሪያ እስከማይሆን ድረስ አንድ ቦታ ማጥፋት መደምሰስ ማለት ነው።

  • ሰውን አስመልክቶ ጥቅም ላይ ከዋለ፣ “ባድማ” ጥፋትን፣ ብቸኝነትንና ሐዘንን ያመለክታል።
  • “ወና ማድረግ” የሚለው ሐረግ መተው ወይም መረሳት ማለት ነው።
  • እህል ሲያበቅል የነበረ ቦታ ባድማ ከሆነ ተባይችን ወይም ወራሪ ሠራዊትን የመሳስሉ እህሉን የሚያጠፉ ነገሮች አሉ ማለት ነው።
  • “ባድማ አካባቢ” ጥቂት እህል ወይም አትክልት ብቻ የሚያድጉበት በመሆኑ ብዙ ሰዎች የማይኖሩበት ቦታ ማለት ነው።
  • ማኅበረ ሰቡ ያገለላቸው የቆዳ በሽታ ያለባቸው ሰዎችና የመሳሰሉትና አደገኛ አራዊት የሚኖሩበት “ባድማ ምድር” ወይም “ጠፍ መሬት” ይባላል።
  • አንድ ከተማ “ወና ሆኖአል” ከተባለ ሕንፃዎች ፈራርሰዋል ወይም ተሰርቀዋል፤ ሕዝቡም በምርዶ ተወስደዋል ማለት ነው። ከተማው ባዶ ሆኖአል፤ ሁሉም ነገር ወድሞአል ማለት ነው። ይህ ማውደም፣ ማጥፋት ከሚለው ጋር ተመሳሳይ ትርጕም ቢኖረውም፣ የበለጠ አጽንዖት የሚሰጠው ባዶ መሆኑን ነው።
  • እንደ ዐውዱ ሁኔታ፣ “ጥፋት” ወይም፣ “ውድመት” ወይም፣ “መደምሰስ” ወይም፣ “የተተወና ፈላጊ የሌለው” ተብሎ መተርጎም ይችላል።