am_tw/bible/other/defile.md

1.4 KiB

ማርከስ፣ መርከስ

“ማርከስ” እና፣ “መርከስ” የተሰኙት ቃሎች መበከልን ወይም በከፍተኛ ደረጃ መቆሸሽን ያመለክታሉ። አንድ ነገር ከአካላዊ፣ ከግብረ ገባዊ ወይም ከሃይማኖታዊ ሥርዓት ጋር በተያያዘ ርኵስ ተብሎ ሊጠራ ይችላል።

  • እርሱ፣ “ርኵስ” ወይም “ያልተቀደሰ” ያለውን በመብላት ወይም በመንካት ራሳቸውን እንዳያረክሱ እግዚአብሔር እስራኤላይውያንን አስጠንቅቆ ነበር።
  • የሞቱ አካሎችና ተላላፊ በሽታዎችን የመሳሰሉ ነገሮችን እግዚአብሔር ርኵሳን ብሏቸዋል፤ እነርሱን የሚነኩ ሰዎች ይረክሳሉ።
  • ከዝሙት ኃጢአት እንዲርቁ እግዚአብሔር እስራኤላውያንን አዞአል። ይህ ኃጢአት ያረክሳችዋል፤ በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት እንዲያጡ ያደርጓቸዋል።
  • የተወሰኑ ሥርዓቶችን በመፈጸም እንደ ገና ንጹሕ እስኪሆን ድረስ ለጊዜውም ቢሆን ሰውን የሚያረክሱ ከአካል የሚወጡ ነገሮች ነበር።
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ አንድን ሰው በእውነት የሚያረክሱት ኃጢአተኛ ዐሳብና ተግባር እንደ ሆኑ ኢየሱስ አስተምሮአል።