am_tw/bible/other/criminal.md

787 B

ወንጀል፣ ወንጀለኛ

“ወንጀል” ብዙውን ጊዜ የሚያመለክተው የአንድ አገርን ወይም መንግሥትን ሕግ የማፍረስ ኃጢአትን ነው። እንዲህ ያለውን በደል የፈጸመ ሰው ወንጀለኛ ይባላል።

  • ሰውን መግደል ወይም የሌላውን ንብረት መስረቅ ወንጀል ከሚባሉት ጥቂቶቹ ናቸው።
  • ብዙውን ጊዜ ወንጀለኛ እስር ቤት ወይም ወህኒ ቤት ውስጥ ተጠብቆ ይቀመጣል።
  • መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ከፈጸሙት በደል የተነሣ ሊበቀሏቸው ከሚፈልጉ ሰዎች ለመሸሽ ወንጀለኞች ከአንዱ ቦታ ወደ ሌላው ይቅበዘበዙ ነበር።