am_tw/bible/other/corrupt.md

647 B

ብልሹ፣ ብልሽት

“ብልሹ” እና፣ “ብልሽት” የሰዎችን ክፋትና ግብረ ገባዊ ዝቅጠት ያመለክታል።

  • ቃል በቃል ሲወሰድ፣ “ብልሹ” ማለት፣ “የተጣመመ” ወይም በግብረ ገባዊ ይዞታው “የወደቀ” ማለት ነው።
  • ብልሹ ሰው ከእውነት ወደ ኋላ የተመለሰና ወራሳ ወይም ጸያፍ ነገሮችን የሚያደርግ ሰው ነው።
  • አንድን ሰው ማበላሸት ወራዳና ጸያፍ ነገሮች እንዲያደርግ በዚያ ሰው ላይ ተጽዕኖ ማድረግ ማለት ነው።