am_tw/bible/other/consume.md

1.0 KiB

መጨረስ

ቃል በቃል ሲወሰድ እስኪያልቅ ድረስ አንድን ነገር መጠቀም ማለት ሲሆን በርካታ ምሳሌያዊ ትርጕሞችም ይኖሩታል።

  • መጸሐፍ ቅዱስ ውስጥ፣ “መጨረስ” የሚለው ቃል ብዙውን ጊዜ ነገሮችን ወይም ሰዎችን ማጥፋት ይመለከታል።
  • እሳት ነገሮችን እንዲጨርስ (እንደሚበላ) ሲነገር ዐመድ እስከሆኑ ድረስ እቃጥሎ ይፈጃቸዋል ማለት ነው።
  • እግዚአብሔር፣ “የሚባላ እሳት” ተብሏል፤ ይህ ኃጢአት ላይ ያለውን ቊጣ የሚገልጽ ነው። ቊጣው በንስሐ ይማይመለሱ ኃጢአተኛ ላይ ከባድ ቅጣት ያመጣል።
  • ምግብ መጨረስ እስኪያልቅ ድረስ መብላት ወይም መጠጣት ማለት ነው።
  • “ምድሪቱን በላ” የሚለው ሐረግ፣ “ምድሪቱን አጠፋ” ተብሎ መተርጎም ይችላል።