am_tw/bible/other/concubine.md

752 B

ዕቁባት

ዕቁባት ቀድሞውኑ ሚስት ያለችው ወንድ ሁለተኛ ሚስት ናት። ብዙውን ጊዜ ዕቁባት የሰውየው ሕጋዊ ሚስት አትሆን።

  • በብሉይ ኪዳን ዘመን ዕቁባት የሚሆኑት እንስት ባሪያዎች ነበሩ።
  • በግዢ፣ በጦር ጊዜ ድል በማድረግ ወይም ለዕዳ በሚደረግ ክፍያ ዕቁባት ማግኘት ይቻላል።
  • አንድ ንጉሕ ብዙ ዕቁባቶች ካሉት ብዙውን ጊዜ የኃይሉና የሥልጣኑ ምልክት ተደርጎ ይወሰድ ነበር።
  • ዕቁባት የመያዝ ልምምድ ከእግዚአብሔር ፈቃድ የሚጻረር መሆኑን አዲስ ኪዳን ያስተምራል።