am_tw/bible/other/clothed.md

1.1 KiB

መልበስ፣ ለበሰ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በምሳሌያዊ መልኩ ጥቅም ላይ ከዋ፣ “ለበሰ” አንድ ነገር፣ “ተቀዳጀ” ወይም አንድ ነገር ታጠቀ ወይም በአንዳች ሁኔታ ዝግጁ ሆነ ማለት ነው። አንድ ነገር፣ “መልበስ” አንድ ዐይነት ፀባይ ወይም ባሕርይ አዳበረ ማለት ነው።

  • የምትለብሱት ልብስ ውጫዊ አካላችሁን እንደሚሰፍንና ለሰው ሁሉ እንደሚታይ፣ አንድ ዓይነት ባሕርይ፣ “ስትለብሱም” ሌሎች ሰዎች በቀላሉ ያዩታል። “ትሕትናን መልበስ” ሰው ሁሉ በቀላሉ እንዲያየው ተግባራችሁና አናኗራችሁ ሁሉ ትሕትናን የሚያንጸባርቅ ይሆናል።
  • “ከላይ ኃይል መልበስ” ሲባል ከላይ የሚመጣ ኃይል መቀበል ማለት ነው።
  • ቃሉ፣ “እፍረት መከናነብ” ወይም፣ “ውርደት ልበሱ” የተሰኙትን የመሳሰሉ አሉታዊ ነገሮችን ለማመልከትም ይጠቅማል።