am_tw/bible/other/chiefpriests.md

943 B

የካህናት አለቆች

ኢየሱስ በዚህ ምድር በነበረ ጊዜ የካህናት አለቆች ከፍ ያለ ሥልጣን የነበራቸው የአይሁድ ሃይማኖት መሪዎች ነበሩ።

  • የካህናት አለቆች ቤተ መቅደስ ውስጥ በሚደረገው የአምልኮ አገልግሎት ማንኛውም ነገር ላይ ኃላፊነት ነበራቸው፤ ለቤተ መቅደስ የሚሰጠውን ገንዘብ የሚቆጣጠሩትም እነርሱ ነበሩ።
  • ከተራዎቹ ካህናት የበለጠ ደረጃና ሥልጣን ነበራቸው። ከእነርሱ የሚበልጥ ሥልጣን የነበረው ሊቀ ካህኑ ብቻ ነበር።
  • የካህናት አለቆች ከኢየሱስ ዋነኛ ጠላቶች ጥቂቶቹ ሲሆኑ፣ እርሱን እንዲይዙና እንዲገድሉት ሮማውያን መሪዎች ላይ ከባድ ተጽዕኖ ያደረጉ እነርሱ ነበሩ።