am_tw/bible/other/beast.md

1.5 KiB

አውሬ

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙውን ጊዜ ስለሌላ “እንስሳ” ለመናገርም ጥቅም ላይ ይውል ነበር

  • የዱር አውሬ በነጻነት ጫካ ውስጥ ወይም ገላጣ ሜዳዎች ላይ የሚኖርና ሰዎች ለማዳ ያላደረጉት የእንስሳ ዓይነት ነው
  • ለማዳ አውሬ ሰዎች ጋር የሚኖርና ምግብ ለመሆን የሚጠበቅ ወይም እርሻን ለመሳሰሉ ሥራዎች የሚያገለግል እንስሳ ነው። “የቤት እንስሳ” የሚለው ቃል እንዲህ ያሉትን እንስሳት ለማመልከት ጥቅም ላይ ይውላሉ
  • የብሉይ ኪዳኑ ትንቢተ ዳንኤልና የአዲስ ኪዳኑ የዮሐንስ ራእይ ክፉ ኅይሎችንና እግዚአብሔርን የሚቃወሙ ባለሥልጣኖችን የሚወክሉ አራዊት ያሉባቸው ራእዮችን ይዘዋል።
  • ከእነዚህ አራዊት አንዳንዶቹ ከአንድ በላይ ራሶችና ብዙ ቀንዶች ያሏቸው ያልተለመዱ ዓይነት ፍጥረቶች ነበሩ። ብዙውን ጊዜ ትልቅ ሥልጣንና ኅይል ያላቸው ሲሆኑ፥ አገሮችን፥ ሕዝቦችንና ሌሎች የፖለቲካ ኅይሎችን ይወክሉ ነበር
  • እነዚህን ቃሎች ለመተርጎም እንደ ዐውዱ አገባብ “ፍጡራን” ወይም፥ “ፍጡር ነገሮች” ወይም፥ “እንስሳት” ወይም፥ “የዱር እንስሳት” ማለት ይቻላል