am_tw/bible/other/bearanimal.md

803 B

ድብ

ድብ ጥቁር ቡናማ ጠጉርና ጠንካራ ጥርሶችና ጥፍሮች ያሉት ባለአራት እግር ግዙፍ እንስሳ ነው። መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን ድብ በእስራኤል በብዛት ይገኝ ነበር

  • እነዚህ አራዊት የሚገኙት ጫካዎች ውስጥና ተራራማ አካባቢዎች ነበር፤ ዓሶችን፥ ጥቃቅን ነፍሳትንና ተክሎችን ይመገባሉ
  • በብሉይ ኪዳን ድብ የብርታትና ጥንካሬ ምሳሌ ተደርጎ ይቀርባል
  • በጎች ይጠብቅ በነበረ ጊዜ እረኛው ዳዊት ከድብ ጋር ታግሎ አሸንፎ ነበር
  • ሁለት ድቦች ከጫካ መጥተው ኤልሳዕ ላይ ያላገጡ በርካታ ልጆችን ገደሉ