am_tw/bible/other/assembly.md

1.6 KiB

ስብሰባ(ጉባኤ)፥ መሰብሰብ

“ስብሰባ(ጉባኤ)” የሚለው ቃል ችግሮች ላይ ለመወያየት፥ ምክር ለመስጠትና ውሳኔ ለማሳለፍ በአንድነት የተሰበሰቡ ሰዎችን ያመለክታል

  • አንድ ስብሰባ በመደበኛነት የተደራጀ ሕጋዊነት ያለው አካል ሊሆን ይችላል ወይም ደግሞ ለተወሰነ ዓላማ ወይም ወቅት በአንድነት የሚገናኝ ጊዜያዊ የሰዎች ስብስብ ሊሆን ይችላል።
  • በብሉይ ኪዳን ዘመን፥ “የተቀደሰ ስብስባ (ጉባኤ)” የሚባል የተለየ ዐይነት ስብሰባ ነበር፤ ይህ የእስራኤል ሕዝብ ያህዌን ለመምለክ በአንድነት የሚገናኙበት ጊዜ ነበር።
  • አንዳንድ “ስብሰባ(ጉባኤ)” የሚለው ቃል በአጠቃላይ እንደማኅበረሰብ እስራኤላውያንን ያመለክታል።
  • ግዙፍ የጠላት ወታድሮች ክምችት አንዳንዴ “ስብሰባ(ጉባኤ) ተብሎ ይጠራል። ይህን ሰራዊት በማለት መተርጎም ይቻላል።
  • አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን ኢየሩሳሌምን በመሳሰሉ ዋና ዋና ከተሞች ይኖሩ የነበሩ 70 የአይሁድ መሪዎች ስብሰባ አንዳንድ ሕግ ነክ ጉዳዮችን ለመወሰንናበሰዎች መካከል ለተፈጠረ አለመግባባት መፍትሔ ለመስጠት ይሰበሰቡ ነበር። ይህ ስብሰባ ሳንሐድሪን ወይም “ሸንጎ” በመባል ይታወቅ ነበር።