am_tw/bible/other/amazed.md

1.2 KiB

መደነቅ፣ መገረም

እነዚህ ቃሎች “አንድ የተለየ ነገር በመደረጉ መደነቅን” ነው የሚያመለክቱት።

  • እነዚህ ቃሎች የተተረጎሙት፣ “በመደነቅ መመታት” ወይም፣ “ከራስ ውጪ መሆን” የሚል ሐሳብ ካላቸው የግሪክ ፈሊጣዊ አነጋገር ነው። እነዚህ ፈሊጣዊ አነጋገሮች አንድ ሰው በጣም መገረሙን ወይም መደንገጡን ያመለክታሉ። ሌሎች ቋንቋዎችም ይህን የሚገልጽ ፈሊጣዊ አነጋገር ሊኖራቸው ይችላል።
  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙውን ጊዜ የመደነቅ ወይም የመገረም ምክንያት ሲሆን የሚታየው እግዚአብሔር ብቻ ማድረግ የሚችለው ተአምር ነው።
  • ብዙውን ጊዜ የእነዚህ ቃሎች ትርጕም ፍጹም ያልተጠበቀና ይሆናል ተብሎ ያልታሰበ ነገር ከመሆኑ የተነሣ ግራ የመጋባት ስሜትንም ይጨምራል።
  • እነዚህን ቃሎች ለመተርጎም ሌሎች ቃሎች “በጣም መገረም” ወይም፣ “በጣም መደንገጥ” የሚሉት ሊሆኑ ይችላሉ።