am_tw/bible/other/12tribesofisrael.md

1.2 KiB

አሥራ ሁለት የእስራኤል ነገዶች

አሥራ ሁለት የእስራኤል ነገዶች የተባሉት የያዕቆብ ልጆችና የእነርሱ ዘሮች ናቸው።

  • ያዕቆብ የአብርሃም የልጅ ልጅ ነበር፤ በኋላ እግዚአብሔር ስሙን እስራኤል አለው።
  • የነገዶቹ ስም፣ ሮቤል፣ ስምዖን፣ ሌዊ፣ ይሁዳ፣ ዳን፣ ንፍታሌም፣ ጋድ፣ አሴር፣ ይሳኮር፣ ዛብሎን፣ ዮሴፍና ብንያም ናቸው።
  • እግዚአብሔርንና ሕዝቡን ለማገልገል የተለዩ የካህናት ነገድ በመሆናቸው፣ የሌዊ ነገድ ከነዓን ውስጥ ምንም ርስት አልተሰጣቸውም ነበር።
  • ዮሴፍ በሁለት ልጆቹ ማለት በኤፍሬምና በምናሴ በኩል ዕጥፍ የርስት ድርሻ ተቀብሏል።
  • የነገዶቹ ዝርዝር መጠነኛ ልዩነት የተደረገላቸው ክፍሎች መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አሉ። ለምሳሌ አንዳንድ ጊዜ ሌዊ፣ ዮሴፍ ወይም ዳን ዝርዝሩ ውስጥ አይገኙም፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ ሁለቱ የዮሴፍ ልጆች ኤፍሬምና ምናሴ ዝርዝሩ ውስጥ ይካተታሉ።