am_tw/bible/names/timothy.md

1.2 KiB

ጢሞቴዎስ

ጢሞቴዎስ እርሱ በነበረበት ልስጥራ ከተማ ጳውሎስ ባገለገለ ጊዜ በክርስቶስ ያመነ ወጣት ሰው ነበር። በኋላም ጳውሎስ ባደረገው በርካታ ሐዋርያዊ ጉዞ አብሮት ነበር፤ የአዲስ አማኞች ማኅበረ ሰብ መጋቢ በመሆንም አገልግሏል።

  • አያቱ ሎይድና እናቱ አውንቅ በክርስቶስ ያመኑ አይሁዳውያን ቢሆኑም፣ አባቱ ግሪካዊ ነበር።
  • ጢሞቴዎስ በግማሽ ጎኑ አይሁዳዊ ስለ ነበር እነርሱን ቅር ሲያሰኝ ከአይሁድ ጋር ተገናኝቶ እንዲያገልግላቸው ጳውሎስ ገረዘው።
  • ጳውሎስና የቤተ ክርስቲያን ሽማግሌዎች እጃቸውን በመጫንና በጸሎት ወግ ባለው ሁኔታ ጢሞቴዎስን ሾሙት።
  • አዲስ ኪዳን ውስጥያሉትን አንደኛና ሁለተኛ የጢሞቴዎስ መልእክቶች ጳውሎስ የጻፈው የአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ወጣት መሪ ለነበረው ጢሞቴዎስ መመሪያ ለመስጠት ነበር።