am_tw/bible/names/shiloh.md

1.1 KiB

ሴሎ

ሴሎ በኢያሱ መሪነት እስራኤላውያን አሸንፈው የያዟት በግንብ የተከበበች የከነዓናውያን ከተማ ነበረች

  • የሴሎ ከተማ የሚገኘው ከዮርዳኖስ ወንዝ በስተ ምዕራብና ከቤቴል ከተማ ሰሜን ምሥራቅ ነበር
  • ኢያሱ እስራኤልን እየመራ በነበረ ዘመን የሴሎ ከተማ የእስራኤላውያን መሰብሰቢያ ነበረች
  • ከምድረ ከነዓን ለእያንዳንዳቸው የሚሰጠውን ርስት ድርሻ ከኢያሱ ለመስማት አሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች በሴሎ ተሰብስበው ነበር
  • በኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ ከመሠራቱ በፊት እስራኤላውይን ለእግዚአብሔር መሥዋዕት ለማቅረብ ወደሴሎ ይመጡ ነበር
  • ሳሙኤል ሕፃን እያለ እርሱን ለጌታ ለመስጠት እናቱ ሐና ወደሴሎ ወስዳው ነበር። እግዚአብሔርን ስለማገልገል እየተማረ እዚያ ከካህኑ ከዔሊ ጋር ቆየ