am_tw/bible/names/samuel.md

814 B

ሳሙኤል

ሳሙኤል የመጨረሻው የእስራኤል መስፍን እና ነቢይ ነበር፤ የእስራኤል ንጉሥ እንዲሆኑ ሳኦልንና ዳዊትን የቀባው እርሱ ነበር

  • ሳሙኤል አርማቴም በሚባል አገር ይኖሩ የነበሩ የሕልቃና እና የሐና ልጅ ነበር
  • ሐና መካን ነበረች፤ ሳሙኤልን የወለደችው ወንድ ልጅ እንዲሰጣት ለእግዚአብሔር ባቀረበችው ጸሎት መልስ ነበር
  • ሐና ባቀረበችው ጸሎት ልጇን ለእግዚአብሔር ለመስጠት ቃል ገብታ ነበር።
  • ሳሙኤል ሕፃን በነበረ ጊዜ ካሕኑ ዔሊን በቤተ መቅደስ እንዲረዳ በገባችው ቃል መሠረት ወደዚያ ወሰደችው