am_tw/bible/names/samaria.md

1.4 KiB

ሰማርያ፣ሳምራዊ

ሰማርያ ለእስራኤል ሰሜናዊ አካባቢ ላለው ከተማና አካባቢው የተሰጠ ስም ነው። ይህ አካባቢ በምዕራብ በሳሮን ሜዳማ ቦታና በምሥራቅ በኩል በዮርዳኖስ ወንዝ መካከል ይገኛል

  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ የሰሜናዊ እስራኤል መንግሥት ዋና ከተማ ነበር። በኋላ ላይ ዙሪያውን ያለው አካባቢም ሰማርያ ተባለ
  • አሦራውያን ሰሜናዊውን የእስራኤል መንግሥት ባሸነፉ ጊዜ እዚያ የነበሩ እስራኤላውያን ወደ ተለያዩ የአሦር ከተማ ወሰዷቸው።
  • አሦራውያን ብዙ የባዕድ አገር ሰዎች ወደሰማርያ በማምጣት ከዚያ የተወሰዱ እስራኤላውያን ቦታ ላይ አሰፈሯቸው
  • አንዳንድ እስራኤላውያን ከእነዚያ ከባዕድ አገር ከመጡ ሰዎች ጋር ተጋቡ፤ ከእነርሱ የተወለዱት ሳምራውያን ተባሉ
  • ከፊል አይሁድ በመሆናቸውና የአረማውያን አማልክትን ያመልኩ ስለነበር አይሁድ ሳምራውያንን ይንቋቸው ነበር
  • አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን ሰማርያ በሰሜን ከገሊላ ጋር፣ በደቡብ ከይሁዳ ጋር ይዋሰን ነበር