am_tw/bible/names/rahab.md

613 B

ረዓብ

ረዓብ እስራኤላውያን ኢያሪኮን ሲያጠቁ እዚያ የነበረች ሴት ነበረች። አመንዝራም ነበረች።

  • እስራኤላውያን ኢያሪኮን ከማጥቃታቸው በፊት ኢይሪኮን ለምሰለል ሲመጡ ረዓብ ሁለቱን እስራኤላውያን ደበቀች። አምልጠው ወደ እስራኤላውያን ሰፈር እንዲመለሱም ረዳቻቸው።
  • ረዓብ በያህዌ አመነች፤ ኢያሪኮ ስትደመሰስ እርሷና ቤተ ሰቧም ዳኑ። ከእስራኤላውያን ጋር አብረው ኖሩ።