am_tw/bible/names/philistines.md

839 B

ፍልስጥኤማውያን

ፍልስጥኤማውያን ፍልስጥኤም በመባል በሚታወቀው የሜድትራንያን ባሕር ዳርቻ አካባቢ የሚኖሩ ሕዝብ ናቸው። የስማቸው ትርጕም፣ “የባሕር ሰዎች” ማለት ነው።

  • የአሽዶድ ከተማ የፍልስጥኤም ሰሜናዊ ክፍል ስትሆን፣ የጋዛ ከተማ ደግሞ ደቡባዊ ክፍል ነበረች።
  • ፍልስጥኤማውያን ይበልጥ የሚታወቁት ከእስራኤል ጋር ለብዙ ዓመት ባደረጉት ጦርነት ነው።
  • አብዛኛውን ጊዜ ከፍልስጥኤማውያን ጋር የሚደረገውን ጦርነት የመራ ንጉሥ ዳዊት ሲሆን፣ ገና ወጣት እያለ ፍልስጥኤማዊው ጦረኛ ጎልያድን አሸንፎ ነበር።