am_tw/bible/names/philip.md

1.0 KiB

ፊልጶስ (ወንጌላዊው)

በኢየሩሳሌም በነበረችው የጥንት ቤተ ክርስቲያን ፊልጶስ ለድኾችና ችግረኛ ክርስቲያኖች በተለይም ለመበለቶች ጥንቃቄ እንዳይደርጉ ከተመረጡ ሰባት መሪዎች አንዱ ፊልጶስ ነበር።

  • ከኢየሩሳሌም ወደ ጋዛ በሚወስደው መንገድ ላገኘው ኢትዮጵያዊ ጨምሮ በይሁዳና በገሊላ አውራጃዎች ውስጥ ለነበሩ ብዙ ከተማ ሰዎች ወንጌልን እንዲያዳርስ እግዚአብሔር በፊልጶስ ተጠቅሟል።
  • ከዓመታት በኋላ ፊልጶስ በቂሣርያ እየኖረ ሳለ ጳውሎስና ጓደኞቹ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመለሱ ያረፉት እርሱ ቤት ውስጥ ነበር።
  • ወንጌላዊው ፊልጶስ የኢየሱስ ሐዋርያ ከነበረው ፊልጶስ የተለየ ሰው እንደ ነበር አብዛኞቹ የመጽሐፍ ቅዱስ ምሁራን ይስማማሉ።