am_tw/bible/names/persia.md

957 B

ፋርስ፣ ፋርሳውያን

ፋርስ በ550 ዓቅክ ታላቁ ቂሮስ የመሠረተው መንግሥት ነው። ማዕከሉ የነበረው የአሁኗ ዘመን ኢራን ያለችበት ቦታ ላይ ነበር። የፋርስ ነዋሪዎች፣ “ፋርሳውያን” ይባላሉ።

  • የፋርስ መንግሥት በጣም ሰፊና ኀያል ነበሩ።
  • በንጉሥ ቂሮስ ትእዛዝ አይሁድ ከባቢሎን ምርኮ ነጻ ሆኑ፤ የፋርስ መንግሥት ባደረገው እገዛ የኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ እንደ ገና ተሠራ።
  • ዕዝራና ነህምያ የኢየሩሳሌምን ቅጥር እንደ ገና ለመሥራት ወደ ኢየሩሳሌም ሲመለሱ የፋርስ መንግሥትን እየገዛ የነበረው ንጉሥ አርጤክስስ ነበር።
  • ንጉሥ አርጤክስስን በማግባቷ አስቴር የፋርስ መንግሥት ልዕልት ሆነች።