am_tw/bible/names/miriam.md

1.2 KiB

ማርያም

ማርያም የአሮንና የሙሴ ታላቅ እኅት ነበረች።

  • ማርያም ትንሽ ልጅ እያለች በቅርጫት ዐባይ ወንዝ ዳር ቄጤማዎች መካከል የተጣለው ታናሽ ወንድሟ ሙሴን በዐይኗ እንድትከታተል እናቷ ነግራት ነበር። የፈርዖን ልጅ ሕፃኑን አግኝታ የሚያሳድገው ሰው እየፈለገች በነበረች ጊዜ ማርያም፣ የሙሴን እናት አመጣችላት።
  • እስራኤላውያን ከግብፃውያን አምልጠው ቀይ ባሕርን ሲሻገሩ እስራኤላውያንን ወደ ደስታና ወደ ምስጋና ሽብሸባ የመራች ማርያም ነበርች።
  • ከዓመታት በኋላ እስራኤላውያን በምድረ በዳ በነበሩ ጊዜ ሙሴ ኢትዮጵያዊት ሴት በማግባቱ ማርያምና አሮን ደስ አልተሰኙም፣ እርሱን በተመለከተ መጥፎ ነገር መናገር ጀመሩ።
  • ሙሴ ላይ ክፉ በመናገር ባሳየችው ዐመፅ እግዚአብሔር ማርያም ላይ ለምጽ እንዲወጣ አደረገ። በኋላ ግን ሙሴ ለእርሷ በመማለዱ እግዚአብሔር ፈውሷታል።