am_tw/bible/names/mesopotamia.md

908 B

መስጴጦምያ፣ አራም ናሐራይም

መስጴጦምያ በኤፍራጥስና በጤግሮስ ወንዞች መካከል ያለ ምድር ነው። ስፍራው የዘመኑ ኢራቅ ያለችበት ቦታ ነበር።

  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ ይህ አካቢ አራም ናሐራይም ይባል ነበር።
  • “መስጴጦምያ” ማለት፣ “በሁለት ወንዞች መካከል” ማለት ነው። “አራም ናሐራይም” ማለት፣ “ባለ ሁለት ወንዞች” ማለት ነው።
  • ወደ ምድረ ከነዓን ከመንቀሳቀሱ በፊት አብርሃም ዑር እና ካራን በተባለት የመስጴጦምያ ከተሞች ይኖር ነበር።
  • ባቢሎን መስጴጦምያ ውስጥ የነበረች ጠቃሚ ከተማ ናት።
  • “ከለድ” ተብሎ የሚጠራውም አካባቢ መስጴጦምያ ውስጥ ነበር።