1.8 KiB
1.8 KiB
መልከጼዴቅ
አብርሃም በነበረበት ዘመን መልከጼዴቅ፣ በኋላ፣ “ኢየሩሳሌም” ተብላ የተጠራችው የሳሌም ከተማ ንጉሥ ነበር።
- የመልከጼዴቅ ስም ትርጉም፣ “የጽድቅ ንጉሥ” ማለት ነው፤ “የሳሌም ንጉሥ” የተሰኘው መጠሪያውም፣ “የሰላም ንጉሥ” ማለት ነው።
- “የልዑል አምላክ ካህን” ተብሎም ተጠርቷል።
- መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ መልከጼዴቅ መጀመሪያ የተጠቀሰው አብራም የወንድሙን ልጅ ሎጥን ብርቱ ከህልኑ ነገሥታት እጅ አስጥሎ ሲመለስ፣ ለአብራም እንጀራና ወይን የሰጠው ጊዜ ነበር። አብራምም ከድሉ ካገኘው ሁሉ አንድ አሥረኛውን ለመልከጼዴቅ ሰጠው።
- አዲስ ኪዳን ውስጥ መልከጼዴቅ አባትና እናት እንደሌለው ተነግሯል። እርሱ ካህንና ለዘላለም የሚነግሥ ንጉሥ ነው። በእግዚአብሔር ልጅ፣ “ተመስሎ” እንደሚኖርም ተነግሯል።
- ኢየሱስ፣ “በመልከጼዴቅ ክህነት” መሠረት ካህን እንደ ሆነ አዲስ ኪዳን ይናገራል። እንደ ሌሎቹ እስራኤላውያን ካህናት ኢየሱስ ከሌዊ ዘር አልተወለደም። የእርሱ ክህነት በቀጥታ ከእግዚአብሔር ነበር።
- እነዚህ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥያሉ ገለጻዎችን መሠረት በማድረግ መልከጼዴቅ ዘላለማዊ የሰላምና የጽድቅ ንጉሥ የሆነውንና ሊቀ ካህናችን የሆነውን ኢየሱስ እንዲወክል በእግዚአብሔር የተመረጠ ሥጋ ለባሽ ካህን እንደ ነበር እንረዳለን።