am_tw/bible/names/malachi.md

715 B

ሚልክያስ

ሚልክያስ ወደ እስራኤል ከተላኩት የእግዚአብሔር ነቢያት አንዱ ነው።

  • ሚልክያስ ትንቢት የተናገረው ከባቢሎን ምርኮ መልስ በኋላ የእስራኤል ቤተ መቅደስ እንደ ገና እየተሠራ በነበረበት ዘመን ነበር።
  • ሚልክያስ የነበረው ምናልባት ነህምያና ዕዝራ በሕይወት በነበሩበት ዘመን እንደ ሆነ ይታሰባል።
  • ትንቢተ ሚልክያስ የመጨረሻው የብሉይ ኪዳን መጽሐፍ ሲሆን፣ “ታናናሾቹ ነቢያት” ከሚባሉት አንዱ እንደ ነበር ትውፊት ያመለክታል።