am_tw/bible/names/judea.md

1.4 KiB

ይሁዳ

“ይሁዳ” የሚለው ቃል የመጣው ከአሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች አንዱ ከነበረው ይሁዳ ከሚለው ስም ነው። ጠበብ ባለና ሰፋ ባለ መልኩ ጥቅም ላይ ይውላል።

  • አንዳንዴ ከሙት ባሕር በስተ ምዕራብ በጥንተ እስራኤል ደቡባዊ ክፍል ያለውን ክፍለ ሀገር ብቻ ለማመልከት፣ “ይሁዳ” ጠበብ ባለ መልኩ ጥቅም ላይ ይውላል። አንዳንድ ተርጓሚዎች ይህን ይሁዳ ይሉታል።
  • አንዳንዴ ደግሞ ገሊላን፣ ሰማርያን፣ ፔርያን፣ ኤዶምያስንና ይሁዳን ጨምሮ ያጥንት እስራኤል ክፍለ ሀገሮችን ሁሉ ለማመልከት፣ “ይሁዳ” የሚለው ቃል ጥቅም ላይ ይውላል።

ተርጓሚዎቹ ልዩነቱን በጣም ግልጽ ማድረግ ከፈለጉ፣ ሰፋ ባለ መልኩ የቀረበውን ይሁዳ (ለምሳሌ ሉቃስ 1፥5) “የይሁዳ አገር” በማለት መተርጎም ይችላሉ፤ ጠበብ ባለ መልኩ (ለምሳሌ ሉቃስ 1፥39) ጥቅም ላይ ከዋለ፣ ይህ ቦታ መጀመሪያ የይሁዳ ነገድ የነበረበት የጥንቱ የእስራኤል ምድር አካል ስለነበር፣ “የይሁዳ ክፍለ ሀገር” በማለት መተርጎም ይቻላል።