am_tw/bible/names/judasiscariot.md

1.0 KiB

አስቆሮቱ ይሁዳ

የአስቆሮቱ ይሁዳ ከአሥራ ሁለቱ የኢየሱስ ሐዋርያት አንዱ ነበር። ለአይሁድ መሪዎች ኢየሱስን አሳልፎ የሰጠ እርሱ ነበር።

  • “አስቆሮቱ” የሚለው ፣ ይሁዳ ያደገበትን ከተማ ለማመልከት “ከቂርያት የመጣ” ማለት ሊሆን ይችላል።
  • ይሁዳ ሌባ ነበር፤ የሐዋርያቱ ገንዘብ ያዥ በነበረ ጊዜ ከገንዘቡ ጥቂቱን ለራሱ ጥቅም ይሰርቅ ነበር።
  • ኢየሱስ የሚገኝበትን ቦታ ለሃይማኖት መሪዎቹ በመንገር ይሁዳ ኢየሱስን አሳልፎ ሰጠ።
  • የሃይማኖት መሪዎቹ ኢየሱስ ላይ ሞት በፈረዱ ጊዜ፣ ይሁዳ ኢየሱስን አሳልፎ በመስጠቱ ተጸጸተ፤ ስለዚህም ራሱን ገደለ።
  • መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የኢየሱስን ወንድምና ከደቀመዛሙርቱ አንዱን የመሳሰሉ ይሁዳ የሚባሉ ሰዎች ነበሩ።