am_tw/bible/names/josiah.md

1.1 KiB

ኢዮስያስ

ኢዮስያስ ለሰላሳ እንደ ዓመት የይሁዳን መግሥት የገዛ እግዚአብሔርን የሚፈራ ንጉሥ ነበር። ሕዝቡ በንስሐ እንዲመለሱና ያህዌን እንዲያመልኩ ለማበረታታት ብዙ ነገሮች አድርጓል።

  • አባቱ ንጉሥ አሞን ከተገደለ በኋላ ኢዮስያስ በስምንት ዓመቱ የይሁዳ ንጉሥ ሆነ።
  • በአሥራ ስምንተኛው የአገዛዝ ዘመኑ ንጉሥ ኢዮስያስ የእግዚአብሔርን ቤተመቅደስ እንደገና እንዲሠራ ሊቀካህኑ ኬልቅያስን አዘዘ። ይህ እየተደረገ እያለ የሕጉ መጻሕፍት ተገኙ።
  • የሕጉ መጻሕፍት ሲነበቡለት ሕዝቡ ምን ያህል በእግዚአብሔር ላይ እያመፁ መሆናቸውን በማሰብ ኢዮስያስ በጣም አዘነ። የጣዖት አመልኮ ቦታዎች ሁሉ እንዲፈርሱና የጣዖቶች ካህናትም እንዲገደሉ አዘዘ።
  • እንደገና የፋሲካ በዓል ማክበር እንዲጀምሩ ሕዝቡን አዘዘ።