1.7 KiB
1.7 KiB
ኢያሱ
መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ኢያሱ በመባል የሚታወቁ በርካታ ሰዎች አሉ። በጣም ታዋቂው የነዌ ልጅና የሙሴ ረዳት የነበረው በኋላም የእግዚአብሔር ሕዝብ ሁነኛ መሪ የሆነው ኢያሱ ነበር።
- የተስፋውን ምድር እንዲሰልሉ ሙሴ ከላካቸው አሥራ ሁለት ሰላዮች አንዱ ኢያሱ ነበር።
- ወደተስፋው ምድር ገብተው ከነዓናውያንን እንዲያሸንፉ እግዝአብሔር ለሰጠው ትእዛዝ እንዲታዘዙ እስራኤላውያንን በማበረታታቱ ከካሌብ ጋር ሆኖ ጉብዝናውንና በእግዚአብሔር መተማመኑን አሳይቷል።
- ከብዙ አመት በኋላ ሙሴ ሲሞት የእስራኤልን ሕዝብ እየመራ ወደተስፋው ምድር እንዲገባ እግዚአብሔር ኢያሱን ሾመው።
- ከከነዓናውያን ጋር በተደረገው የመጀመሪያውና ዝነኛው ጦርነት እግዚአብሔር እንደነገረው ኢያሱ እስራኤላውያን ኢያሪኮን እንዲይዙ መርቷል።
- የተስፋውን ምድር መያዝና ምድሪቱን ለእስራኤል ነገዶች ማከፋፈልን ጨምሮ በኢያሱ አመራር ዘመን የሆነው ሁሉ ብሉይ ኪዳን ውስጥ ባለው መጽሐፍ ኢያሱ ተጽፎ ይገኛል።
- በነቢዩ ሐጌ እና በነቢዩ ዘካርያስ መጻሕፍት ኢያሱ የሚባል ሌላ ሰው ተጠቅሷል። ይኸኛው ኢያሱ የኢየሩሳሌም ቅጥሮች ሲሠሩ እገዛ ያደረገ ሊቀ ካህን ነበር። እርሱ የኢዮሴዴቅ ልጅ ነበር።