am_tw/bible/names/joash.md

1.3 KiB

ኢዮአስ

ብሉይ ኪዳን ውስጥ ኢዮአስ ተብለው የሚጠሩ ጥቂት ሰዎች ነበሩ።

  • አንደኛው ኢዮአስ የእስራኤላዊው ጦረኛ የጌዴዎን አባት ነበር።
  • ኢዮአስ ተብሎ የሚጠራው ሌላው ሰው የያዕቆብ ታናሽ ልጅ የብንያም ዘር ነበር።
  • በጣም ታዋቂው ኢዮአስ በሰባት ዓመቱ የይሁዳ ንጉሥ የሆነው ነው። በግድያ ሕይወቱን ያጣው የይሁዳ ንጉሥ የአካዝያስ ልጅ ነበር።
  • በጣም ትንሽ ልጅ ስለነበር ንጉሥ ለመባል ብቁ እስኪሆን ድረስ የኢዮአስ አክስት ደብቃ ከመገደል አዳነችው።
  • በአገዛዝ ዘመኑ መጀመሪያ ላይ ንጉሥ ኢዮአስ ለእግዚአብሔር እየታዘዘ ነበር። በኋላ ግን ለእግዚአብሔር አልታዘዘም፤ እስራኤላውያንም እንደገና ጣዖቶችን መምልክ ጀምሩ።
  • በጦርነት ከቆሰለ በኋላ ንጉሥ ኢዮአስ በሁለት የገዛ ራሱ ባለ ሥልጣኖች ተገደለ።
  • ማስታወሻ፣ ይህ ንጉሥ በዚሁ ዘመን እስራኤልን ከግዛው ንጉሥ ኢዮአስ የተለየ ነው።