am_tw/bible/names/isaac.md

1003 B

ይስሐቅ

ምንም እንኳ በጣም ያረጁ ቢሆኑም ለእነርሱ እንደሚሰጣቸው እግዚአብሔር ለአብርሃምና ለሣራ ቃል የገባላቸው ልጅ ነው።

  • ከአብርሃም ጋር ያደረገው ኪዳን ይስሐቅንና ዘሮችንም ለዘላለም የሚያካትት እንደ ሆነ እግዚአብሔር ቃል ገብቷል።
  • ይስሐቅን መሥዋዕት አድርጎ ለእርሱ እንዲያቀርብለት በመንገር እግዚአብሔር የአብርሃምን እምነት ፈተነ።
  • የይስሐቅ ልጅ ያዕቆብ አሥራ ሁለት ልጆች ነበሩት። በኋላ ላይ ዘሮቻቸው አሥራ ሁለቱ የእስራኤል ነገዶች ሆኑ።
  • ይስሐቅ፣ “ሳቀ” ማለት ነው። እርሱና ሣራ ወንድ ልጅ እንደሚወልዱ እግዚአብሔር ለአብርሃም በነገረው ጊዜ ሁለቱም በጣም አርጅተው ስለ ነበር አብርሃም ሳቀ።