am_tw/bible/names/hilkiah.md

714 B

ኬልቅያስ

ኬልቅያስ በንጉሥ ኢዮስያስ ዘመን የነበረ ሊቀ ካህን ስም ነው።

  • ቤተ መቅደስ በሚታደስበት ጊዜ ሊቀ ካህኑ ኬልቅያስ የሕጉን መጽሐፍ አገኘ፤ መጽሐፉ ወደ ንጉሥ ኢዮስያስ እንዲወስድም አዘዘ።
  • የሕጉ መጽሐፍ በተነበበ ጊዜ ኢዮስያስ በጣም ተነካ፤ ሕዝቡ እንደ ገና ያህዌን እንዲያመልኩና ለሕጎቹም እንዲታዘዙ አደረገ።
  • ኬልቅያስ የተባለው ሌላው ሰው የአልያቂም ልጅ ሲሆን፣ በንጉሥ ሕዝቅያስ ዘመን ቤተ መንግሥት ውስጥ ይሠራ ነበር።