am_tw/bible/names/hezekiah.md

813 B

ሕዝቅያስ

ሕዝቅያስ 13ኛው የይሁዳ ንጉሥ ነበር። በእግዚአብሔር የሚታመንና ለእርሱ የሚታዘዝ ንጉሥ ነበር።

  • በጣም ክፉ ንጉሥ ከነበረው ከአባቱ ከአካዝ በተለየ መልኩ ንጉሥ ሕዝቅያስ የጣዖት አምልኮን ከይሁዳ በማስወገድ እውነተኛ የእግዚአብሔር አምልኮ እንደ ገና እንዲታደስ አደረገ።
  • ንጉሥ ሕዝቅያስ አጥብቆ በጸለየ ጊዜ እግዚአብሔር ከጽኑ ሕመም ፈወሰው፤ በዕድሜውም ላይ 15 ዓመት ጨመረለት።
  • ወደ ፊት የሚሆነውን በተመለከተ ለሕዝቅኤል ምልክት እንዲሆን ጥላው አሥር ደረጃ ወደ ኋላ ተመልሶ ነበር።