am_tw/bible/names/herodias.md

656 B

ሄሮድያዳ

ሄሮድያዳ መጥምቁ ዮሐንስ ባገለገለበት ዘመን ይሁዳን እየገዛ የነበረው ንጉሥ ሄሮድስ (አንቲጳስ) ሚስት ነበረች።

  • መጀመሪያ ላይ ሄሮድያዳ የሄሮድስ ወንድም የፊልጶስ ሚስት ነበረች፤ ይሁን እንጂ ሕጉ ባይፈቅድም ሄሮድስን አግብታለች።
  • ከሕግ ውጪ በሆነው ጋብቻቸው መጥምቁ ዮሐንስ ሄሮድስንና ሄሮድያዳን ገሠጸ። በዚህ ምክንያት ሄሮድስ ዮሐንስን አሳሰረው በኋላም አንገቱ እንዲቆረጥ አደረገ።