am_tw/bible/names/gomorrah.md

875 B

ጎሞራ

ጎሞራ ከባቢሎንያ አካባቢ በስተ ምሥራቅ ባለው በጣም ለም ሸለቆ ውስጥ አንድ ቦታ ላይ የነበረች ከተማ ነበረች።

  • ብዙውን ጊዜ ጎሞራ ከሰዶም ጋር ተያይዛ ትጠቀሳለች፤ የእነዚህ ከተማ ሰዎች በክፉ ሥራቸው የታወቁ ነበር።
  • ሰዶምና ጎሞራ በነበሩበት ቦታ ብዙ ነገሥታት እየተዋጉ ነበር።
  • በሰዶምና በሌሎችም ከተሞች መካከል በተደረገው ግጭት የሎጥ ቤተ ሰብ ተይዞ በተወሰደ ጊዜ ያስጣሏቸው አብርሃምና አብረውት የነበሩ ሰዎች ነበሩ።
  • ይህ ከሆነ በኋላ ብዙም ሳይቆም እዚያ ከነበሩ ሰዎች ኀጢአት የተነሣ እግዚአብሔር ሰዶምና ጎሞራን አጠፋ።