am_tw/bible/names/gilgal.md

1.1 KiB

ጌልጌላ

ጌልጌላ ከኢያሪኮ በስተ ሰሜን ያለች አገር ስትሆን፣ ወደ ከነዓን ለመግባት እስራኤላውያን የዮርዳኖስን ወንዝ ከተሻገሩ በኋላ የሰፈሩባት የመጀመሪያ ቦታ ናት።

  • እነርሱ ከተሻገሩት የዮርዳኖስ ወንዝ ደረቅ ምድር የወሰዳቸውን አሥራ ሁለት ድንጋዮች ኢያሱ የተከለው በጌልጌላ ነበር።
  • ኤልያስ ወደ ሰማይ በሚወሰድበት ጊዜ የዮርዳኖስን ወንዝ ተሻግረው ሲሄዱ ኤልያስና ኤልሳዕ ተነሣሥተው የሄዱት ከጌልጌላ ነበር።
  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ፣ “ጌልጌላ” ተብለው የተጠሩ ሌሎች ጥቂት ቦታዎች ነበር።
  • “ጌልጌላ” ማለት፣ “የድንግይ ክብ” ማለት ነው። እንዲህ የተባለው እዚያ ተሠርቶ በነበረው ክብ ቅርጽ በነበረው መሠዊያ የተነሣ ሊሆን ይችላል። ከሚሽከረከር ነገር የተያያዘ ነገርን የሚያመለክትም ቃል ነው።