am_tw/bible/names/ezekiel.md

851 B

ሕዝቅኤል

ሕዝቅኤል ብዙ አይሁድ ወደባቢሎን በተወሰዱበት የምርኮ ወቅት የነበረ የእግዚአብሔር ነብይ ነው።

  • እርሱና ሌሎች ብዙ አይሁዳውያን በባቢሎን ሰራዊት ከመያዛቸው በፊት ሕዝቅኤል በይሁዳ መንግሥት ውስጥ የሚኖር ካህን ነበር።
  • እርሱና ሚስቱ ባቢሎን ወንዝ አጠገብ ከሃያ ዓመት የበለጠ እየኖሩ እያለ የትንቢት ቃል ለመስማት አይሁድ ወደእርሱ መጡ።
  • ከትንቢቶቹ መካከል ሕዝቅኤል ስለኢየሩሳሌምና ቤተመቅደሱ መደምሰስና እንደገና መሠራት ትንቢት ተናግሮ ነበር።
  • ስለየወደፊቱ የመሲሕ መንግሥትም ትንቢት ተናግሮአል።