am_tw/bible/names/elijah.md

1.1 KiB

ኤልያስ

ኤልያስ በጣም ታዋቅ ከሆኑት የያህዌ ነቢያት አንዱ ነበር። ንጉሥ አክዓብን ጨምሮ ኤልያስ በተለያዩ የእስራኤል ወይም የይሁዳ ነገሥታት ዘመን ነበር ያገለገለው።

  • የሞተውን ልጅ ማስነሣትን ጨምር እግዚአብሔር በኤልያስ በኩል ብዙ ተአምራት አድርጓል።
  • በአል የተሰኘውን ጣዖት በማምለኩ ኤልያስ ንጉሥ አክዓብን ገሥጾታል።
  • እውነተኛው አምላክ ያህዌ ብቻ መሆኑን ለማሳየት ባቀረበው ፈተና ያህዌ የበአል ነቢያትን ተገዳደረ።
  • የኤልያስ ሕይወት ማብቂያ ላይ ገና በሕይወት እያለ በተአምር እግዚአብሔር ወደ ሰማይ ወሰደው።
  • ከመቶ ዓመታት በኋላ ኤልያስ ከሙሴ ጋር፣ ተራራው ላይ ከኢየሱስ ጋር ታየ፤ ወደ ፊት ስለሚሆነው የኢየሱስ መከራና በኢየሩሳሌም ስለ መሞቱ እየተነጋገሩ ነበር።