am_tw/bible/names/edom.md

1.1 KiB

ኤዶም፣ ኤዶማዊ፣ ኤዶሚያ፣ ሴይር፣ ቴማን

ኤዶም፣ የኤሳው ሌላው ስም ሲሆን፣ ኤዶማውያን የእርሱ ዘሮች ናቸው። የኤዶም አገር ኤዶምያ ወይም ሴይር በመባልም ይታወቃል።

  • ኤዶም ተራራማና ከእስራኤል በስተ ደቡብና በስተ ምሥራቅ የሚገኝ ቦታ ነበር።
  • ኤዶም፣ “ቀይ” ማለት ሲሆን፣ ኤሳው ሲወለድ በቀይ ጠጉር ተሸፍኖ እንደ ነበር ለማመልከት ሊሆን ይችላል። ወይም ደግም የበኵርና መብቱን የለወጠበትን ቀይ የምስር ወጥ ለማመልከት ሊሆን ይችላል።
  • ብሉይ ኪዳን ውስጥ ብዙውን ጊዜ የኤዶም ምድር የተጠቀሰው የእስራኤል ጠላይ ከመሆኑ አንጻር ነበር።
  • በኤዶም ላይ የሚመጣውን ጥፋት አስመልክቶ እግዚአብሔር በነቢያት በኩል ብዙ ትንቢቶች ሰጥቷል። ትንቢተ አብድዩ በሙሉ የሚናገረው ኤዶም ላይ ስለማመጣው ፍርድ ነው።