am_tw/bible/names/daniel.md

1.4 KiB

ዳንኤል

ዳንኤል ገና ወጣት እያለ በ600 ዓቅክ በባቢሎን ነጉሥ ናቡከደነፆር በምርኮ የተወሰደ እስራኤላዊ ነቢይ ነበር።

  • ይህ የሆነው ከይሁዳ ምድር ብዙ እስራኤላውያን ለ70 ዓመት የባቢሎን ምርኮኞች በሆኑበት ዘመን ነበር።
  • ዳንኤል፣ ብልጣሶር የሚሰኝ ባቢሎናዊ ስም ተሰጥቶት ነበር።
  • ዳንኤል ለእግዚአብሔር የሚታዘዝ የተከበረና ጻድቅ ሰው ነበር።
  • ዳንኤል የአንዳንድ ባቢሎናውያን ነገሥታትን ሕልም ወይም ራእይ የመፍታት ችሎታ እግዚአብሔር ሰጥቶት ነበር።
  • ከዚህ ችሎታውና ከተከበረው ፀባዩ የተነሣ ዳንኤል በባቢሎን መንግሥት ውስጥ ከፍተኛ አመራር ቦታ ያዘ።
  • ከብዙ ዓመታት በኋላ የዳንኤል ጠላቶች ከንጉሡ በቀር ሌላ ማንም እንዳይመለክ የመከለክል ሕግ እንዲያወጣ ባቢሎናዊው ንጉሥ ዳርዮስን አሳሳቱት። ዳንኤል ግን ወደ እግዚአብሔር መጸለይን አላቋረጠም፤ ስለዚህም ተይዞ ወደ አንበሶች ጉድጓድ ተጣለ። ይሁን እንጂ፣ እግዚአብሔር ስለ ጠበቀው አንበሶቹ አልጎዱትም።