am_tw/bible/names/damascus.md

1.4 KiB

ደማስቆ

ደማስቆ ሶርያ የሚባለው አገር ዋና ከተማ ነው። ዛሬም ቢሆን መጽሐፍ ቅዱስ በተጻፈበት ዘመን የነበረበት ቦታ ላይ ነው ያለው።

  • ደማስቆ ሰዎች ያለ ማቋረጥ ሲኖሩባቸው ከነበሩ ጥንታዊ የዓለም አገሮች አንድ ነው።
  • አብርሃም በነበረበት ዘመን ደማስቆ የአራም መንግሥት ዋና ከተማ ነበር (የነበረው አሁን ሶርያ ያለችበት ቦታ ላይ ነበር)።
  • በመላው ብሉይ ኪዳን በደማስቆ ነዋሪዎችና በእስራኤል ሕዝብ መካከል ስለ ነበረው ግንኙነት የሚያወሱ ብዙ ጥቅሶች አሉ።
  • በርካታ የመጽሐፍ ቅዱስ ትንቢቶች ደማስቆ እንደምትጠፋ ያመልክታሉ። በብሉይ ኪዳን ዘመን አሦር ከተማዋን ያጠፋ ጊዜ እነዚህ ትንቢቶች ተፈጽመው ይሆናል፤ ወይም ደግሞ ይህች ከተማ ሙሉ በሙሉ መውደም ገና ወደ ፊት የሚፈጸም ሊሆን ይችላል።
  • ከአዲስ ኪዳን እንደምንመለከተው ኢየሱስ ፊት ለፊት ከእርሱ ጋር ተገናኝቶ በእርሱ የሚያምን ሰው ባደረገው ጊዜ በኋላ ጳውሎስ የተባለው ፈሪሳዊው ጳውሎስ ክርስቲያኖችን ለማሰር ወደ ደማስቆ እየሄደ ነበር።