am_tw/bible/names/colossae.md

1.4 KiB

ቆላስይስ፣ የቆላስይስ ሰዎች

አዲስ ኪዳን በተጻፈበት ዘመን ቆላስይስ ፍርግያ በምትባለው የሮማውያን ግዛት ውስጥ የነበረች ከተማ ስትሆን በአሁኑ ጊዜ የምትገኘው ከቱርክ ደቡብ ምዕራብ ባለው አካባቢ ነው። የቆላስይስ ሰዎች ቆላስይስ ውስጥ የነበሩ ሰዎች ናቸው።

  • ከሜዲትራንያን ባሕር 100 ማይሎች ርቃ ትገኝ የነበረችው ቆላስይስ በኤፌሶን ከተማና በኤፍራጥስ ወንዝ መካከል ጠቃሚ የንግድ መላለፊያ ነበረች።
  • በሮም እስር ቤት በነበረ ጊዜ በመካከላቸው የነበረውን የሐሰት ትምህርት እንዲያስተካክሉ ጳውሎስ ለቆላስይስ ሰዎች መልእክት ጽፎላቸው ነበር።
  • ይህን መልእክት በጻፈበት ጊዜ ጳውሎስ በቆላስይስ የነበረችው ቤተ ክርስቲያን አልጎበኘም ነበር፣ እዚያ ስለ ነበሩት አማኞች የሰማው የሥራ ባልደረባው ከነበረው ከኤጳፍራ ነበር።
  • ኤጳፍራ የቆላስይስን ቤተ ክርስቲያን የመሠረተ ክርስቲያን አገልጋይ ሳይሆን አይቀርም።
  • የፊልሞን መልእክት ጳውሎስ ለቆላስይስ ለነበረ ባሪያ አሳዳሪ የጻፈው ነበር።