am_tw/bible/names/bethlehem.md

779 B

ቤተልሔም ኤፍራታ

ቤተልሔም ኢየሩሳሌም ከተማ አጠገብ የምትገኝ አንዲት ትንሽ የእስራኤል ከተማ ነበረች። “ኤፍራታ” በመባልም ትታወቃለች፤ ምናልባት የመጀመሪያ ስሟ ይህ ሳይሆን አይቀርም

  • ንጉሥ ዳዊት የተወለደው እዚያ ስለነበር፥ ቤተልሔም፥ “የዳዊት ከተማ” ተብላለች
  • መሲሁ ከ “ቤተልሔም ኤፍራታ” እንደሚመጣ ነብዩ ሚክያስ ተናግሮ ነበር
  • በዚያ ትንቢት ፍጻሜ ከብዙ ዓመቶች በኋላ ኢየሱስ በቤተልሔም ተወለደ
  • ቤተልሔም፥ “የእንጀራ ቤት” ወይም፥ “የምግብ ቤት” ማለት ነው