am_tw/bible/kt/kingdomofgod.md

1.3 KiB
Raw Blame History

የእግዚአብሔር መንግሥት፣ መንግሥተ ሰማይ

“የእግዚአብሔር መንግሥት” እና፣ “መንግሥተ ሰማይ” የሚሉት ሁለቱም የሚያመለክቱት በሕዝቡና በፍጥረት ሁሉ ላይ እግዚአብሔር ያለውን አገዛዝ ነው።

  • ስሙን በቀጥታ ላለ መጥራት ብዙ ጊዜ አይሁድ፣ “ሰማይ” የሚለውን ቃል የሚጠቀምበት እግዚአብሔርን ለማመልከት ነው።
  • አዲስ ኪዳን ውስጥ ከማቴዎስ ወንጌል እንደምንመለከተው “የእግዚአብሔር መንግሥትን” “መንግሥተ ሰማይ” በማለት ጠርቶታል፤ ይህን ያደረገው እየጻፈ የነበረው በዋነኛነት ለአይሁድ ስለሆነ ይሆናል።
  • የእግዚአብሔር መንግሥት የቁሳዊው ዓለም ገዢ እንደ ሆነ ሁሉ በመንፈሳዊ ደረጃም እግዚአብሔር ሕዝቡን እየገዛ እንደ ሆነ ያመለክታል።
  • በጽድቅ እንዲገዛ እግዚአብሔር መሲሑን እንደሚልክ ብሉይ ኪዳን ይናገራል። የእግዚአብሔር ልጅ መሲሑ ኢየሱስ በእግዚአብሔር መንግሥት ለዘላለም ይገዛል።