am_tw/bible/other/warrior.md

931 B

ተዋጊ፣ ወታደር

ሁለቱም ሰራዊት ውስጥ ሆኖ መዋጋትን የሚያመለክቱ በመሆናቸው፣ “ተዋጊ” እና፣ “ወታደር” ትርጕማቸው ተመሳሳይ ነው። ያም ሆኖ ግን፣ መጠነኛ ልዩነትም አላቸው።

  • ብዙ ጊዜ፣ “ተዋጊ” የሚለው በጦር ሜዳ ልምድና ድፍረት ያለውን ሰው የሚያመለክት አጠቃላይና ሰፋ ያለ ቃል ነው።
  • በምሳሌያዊ አነጋገር ያህዌ ራሱ፣ “ተዋጊ” እንደ ሆነ ተነግሯል።
  • “ወታደር” በጣም ግልጽ በሆነ ሁኔታ በአንድ ሰራዊት ውስጥ ወይም ዐውደ ውጊያ ውስጥ የሚዋጋ ሰው ነው።
  • በትርጕምና በአጠቃቀም የተለየ ትርጕም ያላቸው ሁለት ቃላት ሊኖር መቻላቸውን ተርጓሚው ልብ ማድረግ አለበት።