am_tw/bible/other/voice.md

1.2 KiB

ድምፅ

አንድ ሰው ሲናገር ድምፅ ይጠቀማል፤ ስለዚህም ብዙ ጊዜ “ድምፅ” ንግግርን ወይም ሐሳብ ማስተላለፍን ለማመልከት ጥቅም ላይ ይውላል።

  • ምንም እንኳ እርሱ የሰው ዓይነት ድምፅ ባይኖረውም፣ እግዚአብሔር በድምፅ መጠቀሙ ተነግሯል።
  • ድምፅ ሰውን በመወከልም ጥቅም ላይ ውሏል፤ ለምሳሌ፣ “የጌታን መንገድ አዘጋጁ እያለ በምድረ በዳ የሚጮኽ ድምፅ” እንደሚለው ይህንንም፣ “አንድ ሰው ምድረ በዳ ውስጥ ሲጮኽ ተሰማ” በማለት መተርጎም ይቻላል።
  • አንዳንዴ መናገር የማይችሉ ነገሮችን አስመልክቶም “ድምፅ” ጥቅም ላይ የዋለበት ሁኔታ አለ፤ ለምሳሌ እግዚአብሔር የሠራቸው አስደናቂ ፍጥረታት እርሱ ምን ያህል ታላቅ መሆኑን፣ “ድምፅ” አውጥተው እንደሚናገሩ ዳዊት አመልክቷል። ይህም፣ “የፍጥረታቱ ውበት የእግዚአብሔርን ታላቅነት ያሳያል” ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።