am_tw/bible/other/unfaithful.md

1.9 KiB

ያልታመነ፣ አለመታመን

“ያልታመነ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው እንዲያደርግ እግዚአብሔር ያዘዘውን ነገር የማያደርገውን ሰው ነው። እንዲህ ማድረግ አለመታመን ነው።

  • ጣዖትን በማምለካቸውና በሌሎች መንገዶችም ለእግዚአብሔር ባልታዘዙ ጊዜ እስራኤላውያን፣ “ያልታመኑ” ተብለዋል።
  • ከትዳር ጓደኛው ውጪ የግብረ ሥጋ ግንኙነት የሚያደርግ ሰው፣ “ያልታመነ” ይባላል።
  • “ያልታመነ” በሚለው ቃል እግዚአብሔር የተጠቀመው የእስራኤልን ዐመፀኝነት ለማመልከት ነበር። ለእርሱ እየታዘዙ ወይም እርሱን እያከበሩ አልነበረም።
  • መንፈሳዊ ያልሆነ፣ እግዚአብሔርን የማይፈራ፣ እግዚአብሔርን አለመፍራት፣ መንፈሳዊ አለመሆን “መንፈሳዊ ያልሆነ” እና፣ “እግዚአብሔርን የማይፈራ” የተሰኙት ቃሎች እግዚአብሔር ላይ እያመፁ ያለ ሰውን ያመለክታሉ። እግዚአብሔርን ባለማሰብ በክፉ መንገድ መኖር ወይም “እግዚአብሔርን አለመፍራት” መንፈሳዊ አለምሆን ማለት ነው።
  • የእነዚህ ሁሉ ቃሎች ትርጕም በጣም ተመሳሳይ ነው። ይሁን እንጂ፣ “እግዚአብሔርን አለመፍራት” እና፣ “እግዚአብሔርን የማይፈራ” የተባሉት ቃሎች በጣም በባሰበት ሁኔታ እግዚአብሔርን ወይም በእነርሱ ላይ ያለውን ሥልጣን የማይቀበሉ ሰዎችን ያመለክታል።
  • እግዚአብሔርን በማይፈሩ፣ እርሱንና የእርሱን መንገድ ችላ በሚሉት ላይ እግዚአብሔር ይፈርዳል።