am_tw/bible/other/tribute.md

856 B

ግብር

ግብር ከለላ ለማግኘትና በሕዝቦቻቸው መካከል መልካም ግንኙነት እንዲኖር አንድ መንግሥት ወይም ገዢ ለሌላው የሚያቀርበው ስጦታ ነው።

  • ግብር አንድ ገዢ ወይም መንግሥት ከሕዝቡ የሚሰበስበው ገንዘብ ወይም ዋጋ ያለው ሌላ ነገር ሊሆን ይችላል።
  • በጥንት ዘመን ጕዞ ላይ ያሉ ንጉሦች ወይም ገዦች ጥበቃና ከለላ እንዲደረግላቸው ለሚያልፉበት አካባቢ ንጉሥ ወይም ገዢ ግብር ይከፍሉ ነበር።
  • ብዙውን ጊዜ ከገንዘብ ሌላ ምግብ፣ ቅመማ ቅመም፣ ውድ ልብሶች፣ እና ወርቅን የመሳሰሉ የከበሩ ድንጋዮችን ግብር ማቅረብ የተለመደ ነበር።