am_tw/bible/other/tribulation.md

894 B

መከራ

“መከራ” የሚለው ቃል የሚያመለክተው መከራና ጭንቀት ያለበት አዳጋች ጊዜን ነው።

  • እየኖሩ ያሉት የኢየሱስን ትምህርት የሚቃወም ዓለም ውስጥ በመሆኑ ክርስቲያኖች በስደትና ማንኛውም ዐይነት መከራ ባለበት ሁኔታ ውስጥ እንደሚያልፉ አዲስ ኪዳን ይናገራል።
  • ከኢየሱስ ዳግም መምጣት በፊት እግዚአብሔር ለተወሰኑ ዓመታት ቁጣውን በምድር ላይ እንደሚያወርድ ሲያመለክት መጽሐፍ ቅዱስ፣ “ታላቁ መከራ” በሚል ቃል ይጠቀማል።
  • “መከራ” የሚለው ቃል፣ “ታላቅ የመከራ ጊዜ” ወይም፣ “ከባድ ጭንቀት” ወይም፣ “ጽኑ ስደት” በማለት መተርጎም ይቻላል።